አምራች ኢንዲስትሪያሊስቶች በሁለንተናዊ ዘርፉ የሚያጋጥማቸውን ተግዳሮቾች በመፍታት የሃገር ኢኮኖሚን ከመደገፍ ባለፈ ሃገራችንን የአፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በዘርፉ የተሰማሩ አካላት የሚጠበቅባቸውን ድርሻ መወጣት እንዳለባቸው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) ገለጹ።
በቦሌ ለሚ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በተጠናቀቀው የፈረጆች ዓመት ከ900 ሚሊዮን ዶላር በላይ ያስመዘገቡ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ ወደ ስራ መግባታቸውን ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጠና የታለመለትን ሃገራዊ ራዕይና ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጣ በዘርፉ ያሉ ባለድርሻ አካላት ትብብርና ተቀናጅቶ መስራት ወሳኝ መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የማይቋረጥ የኃይል አቅርቦት ለኢንዱስትሪ ልማትና ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) ገለጹ።