ኢትዮጵያ ባለፉት 11 አመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ሁሉንም አይነት ኢንቨስትመንት ተቀብለው ማስተናገድ የሚችሉ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ኢንዱስትሪ ፓርኮች ገንብታ ባለሃብቶችን በማስተናገድ ላይ መሆኗን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኦፐሬሽንና ፓርክ አስተዳደር ዘርፍ ስራ አስፈፃሚ አቶ ፍፁም ከተማ ገለፁ፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን “ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ዝግጁ ነች” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡
በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት ያላቸው የተለያዩ የእንግሊዝ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ልዑካን የቂሊንጦ እና የቦሌ ለሚ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችን የጎበኙ ሲሆን፤ በቆይታቸውም ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር በኢንቨስትመንት ሁኔታዎች ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።
በቻይናው ግዙፍ የፋርማሲዩቲካል ኩባንያ ሂውማንዌል ሄልዝኬር ግሩፕ ሰብሳቢ ደንግ ዌይዶንግ የተመራና 17 ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ የልዑካን ቡድን በቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የሥራ ጉብኝት አደረገ።