• Striving for eco industrial park
logo

በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ ከ10 በላይ ባለሃብቶች ስራ ለመጀመር የሚያስችላቸውን የግንባታ ስራዎች በማከናወን ላይ ይገኛሉ

በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ ከ10 በላይ ባለሃብቶች ስራ ለመጀመር የሚያስችላቸውን የግንባታ ስራዎች በማከናወን ላይ ይገኛሉ

በቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በፋርማሲዩቲካል የኢንቨስትመንት ዘርፍ የሚሰማሩ ከ10 በላይ ባለሃብቶች የግንባታ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ 

የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ስራ አስኪያጅ አቶ ቶሎሳ በዳዳ እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከኮርፖሬሽኑ ጋር ስምምነት ከተፈራረሙ ተቋማት መካከል ከ10 በላይ የሚሆኑት በፋርማሲዪቲካል ኢንቨስትመንት ዘርፍ የሚፈለገውን ደረጃ እና መስፈርት ያሟላ የግንባታ ስራን በማከናወን ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ አሁን ላይ 5 ኩባንያዎች የግንባታ ስራዎችን በማጠናቀቅ ምርት የማምረት እና የሙከራ ምርቶችን  በማምረት ላይ መሆናቸውን የገለጹት  ስራ አስኪያጁ እነዚህ ኩባንያዎች አሁን ላይ ከ4000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል ፈጥረውላቸዋል ብለዋል፡፡

የፋርማሲዪቲካል የኢንቨስትመንት ዘርፍ ከሌሎች የኢንቨስትመንት ዘርፎች በተለየ መልኩ አስገዳጅ ደረጃዎችን ማሟላት የሚጠይቅ በመሆኑ እና የተለየ ጥንቃቄ የሚሻ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ 

 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኑን የኃይል አቅርቦት ለማስፋት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በመመደብ የማስፋፊያ ስራዎች በመስራት  ላይ መሆኑን አቶ ቶሎሳ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

በቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ከ26 በላይ ባለሃብቶች በስራ፤በግንባታ እንዲሁም የመሬት ርክክብ ፈጽመው በተለያየ የስራ ሂደት ላይ ሲሆኑ በቀጣይም በፋርማሲዩቲካል እና በሃይቴክ ኢንቨስመንት ዘርፍ ባለሀብቶችን ተቀብሎ ለማስተናገድ አስፈላጊወን ዝግጅት አድርገው ባለሀብቶችን በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡

#IPDC10thAnniversary
#anniversary
#IPDC
#PMOEthiopia 
#striving_for_eco_industrial_park
#industrialpark
#ecoindustrialpark
#Investment 
#ForeignDirectInvestment
#Importsubstitution
#exportprocessingzone 
#SpecialEconomicZones
#madeinethiopia
#madein 
#exportprocessingzone 
#SpecialEconomicZones
#madeinethiopia
#madein
#InvestInEthiopia
#InvestEthiopia 
#TextileHub 
#PlugAndPlay 
#AfricaRising 
#manufactureinafrica
#kilintospecialeconomiczone

በዌብሳይት - https://ipdc.gov.et/ 
በፌስቡክ - https://www.facebook.com/IPDCEthiopiaofficial 
በትዊተር (ኤክስ) - https://x.com/EthiopiaIpdc 
በቴሌግራም - https://t.me/ipdcofficial 
በሊንክድ ኢን - https://www.linkedin.com/company/ipdcethiopiaofficial 
በኢንስታግራም - https://www.instagram.com/ipdc_et 
በዩቲዩብ - https://www.youtube.com/@IPDCETHIOPIA 
በቲክቶክ - https://www.tiktok.com/@ipdc_ethiopia 
በቴሌግራም ቦት፡- https://t.me/ipdctchatbot
በዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCUHKJP21D0s3OEB30