በኢትዮጵያ ዉስጥ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ተብለዉ የሚታወቁ ወደ አርባ (40) ድርጅቶች ሲኖሩ ከለዉጡ መንግስት የፖለቲካና ኢኮኖሚ ሪፎርም በፊት በመንግስት ልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር(Public Enterprises Holding Agency/PEHA) ክትትልና ቁጥጥር ስር ሆነዉ አስተዳዳሪ ቦርድ እየተሾመላቸዉ ባለቤትነታቸዉም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት( የገንዘብ ሚኒስቴር) ሆኖ በኢኮኖሚዉ ዉስጥ ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና መስሪያ ቤትና በአዲስ አበባ የሚገኙ ቅርንጫፎች የስራ መሪዎችና ሰራተኞች 22ኛውን ዓለም አቀፍ የጸረ ሙስና ቀንን“ትውልድን በሥነ-ምግባር፤ ተቋምን በአሠራር” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች ትናንት አክብረዋል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከአዲስ አበባ ንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ጋር በመተባበር ዓለም ዓቀፍ ደረጃን ያሟላ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን የተቀናጀ የስራ አመራር ስርዓት ለመተግበር የሚያስችል ስልጠና ለዋና መስሪያ ቤት መምሪያ ኃላፊዎች እና ለልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ስራ አስኪያጆች ሰጥቷል፡፡
የድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጠና የታለመለትን ሃገራዊ ራዕይና ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጣ በዘርፉ ያሉ ባለድርሻ አካላት ትብብርና ተቀናጅቶ መስራት ወሳኝ መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡