የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ከ2.7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱ ተገልጿል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ 6 ወራት ከ377 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ያስመዘገቡ 64 ባለሃብቶች ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ኢንዱስትሪ ፓርኮች መሳብ መቻሉ ተገልጿል፡፡
የእቅድ አፈፃፀሙን የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) ፤የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም የስራ መሪዎችና የልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ስራ አስኪያጆች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ባለፉት 6 ወራት ያስመዘገበው የኤክስፖርት እቅድ አፈጻጸም ከእጥፍ በላይ ማደጉ አበረታች መሆኑን የኮርፖሬሽኑ የስራ አመራር ቦርድ ገልጿል፡፡