ኢትዮጵያ ባለፉት 11 አመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ሁሉንም አይነት ኢንቨስትመንት ተቀብለው ማስተናገድ የሚችሉ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ኢንዱስትሪ ፓርኮች ገንብታ ባለሃብቶችን በማስተናገድ ላይ መሆኗን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኦፐሬሽንና ፓርክ አስተዳደር ዘርፍ ስራ አስፈፃሚ አቶ ፍፁም ከተማ ገለፁ፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና ኢንዱስትሪ ፓርኮች የሃገር ውስጥ ባለሃብቶችን ተሳትፎ በማሳደግ የማኑፋክቸሪግ ዘርፉ ለሃገራዊ እድገት የበኩሉን ሚና እንዲያበረክት የሚያስችሉ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑን የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) ገለፁ።
በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ከ8 በላይ ሀገራት የተሰማራው የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ልዑካን ቡድን አባላት ግሩፑ ሀብቱንና የኢንዱስትሪ ልማት እውቀቱን በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በሚተዳደሩ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ላይ ለማዋል ስለሚችልበት አግባብ ከኮርፖሬሽኑ አመራሮች ጋር ተወያይቷል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከCO3 ኢነርጂ ኩባንያ ጋር ከልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች የሚወጡ ተረፈ ምርቶችን ወደ አማራጭ የኃይል ምንጭ በመቀየር ወደ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።